ChatCrawlerпоиск по публичному Telegram Открыть приложение
A

ASTU Network Group ®

сообщение · 2026-08-01 06:30 UTC
I
Фотография
нажмите — покажем
በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ተማሪዎችና የሚያስተምሩ መምህራን ወደ ሌላ ዩኒቨርስቲ " ቀይሩን " የሚል ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ። በትግራይ በሚገኙ አራት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚያማሩ አንዳንድ ተማሪዎችና መምህራን በክልሉ ባለው የጸጥታ ስጋት ምክንያት ወደ ሌሎች የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲዛወሩ አቤቱታ እያቀረቡ እንደሚገኝ ተሰምቷል። ጥያቄው የቀረበው በክልሉ በሚገኙት ፦ - መቐለ ፣ - አክሱም ፣ - ዓዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከሚያምሩ ተማሪዎች እና መምህራን መሆኑ ተመላክቷል። በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት ሓየሎም ስዩም እንደገለጹት፤ ተማሪዎችና መምህራን በጸጥታ ምክንያት የቅሬታ ወረቀት እያስገቡ ቢሆንም፣ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል እስካሁን የተሰጠ የዝውውር ውሳኔም ሆነ የተገባ ቃል አለመኖሩን አስታውቀዋል። |➲| @ASTU_Network
313 ·

Вся лента · оригинал в Telegram

Открыть в Telegram Каталог площадок Искать в ChatCrawler

Слепок открытой публичной ленты из поискового индекса ChatCrawler — «Google по публичному Telegram»; обновляется по мере обхода площадки. Время — UTC.

Только публичный контент, официальный API Telegram. О проекте · Вопросы · Чего мы не делаем · Убрать страницу из выдачи · Каталог