EHPM - Ethiopian Health Professionals' Movement
Фотография
click to show
click to show
እጅግ ልብን የሚሰብር፣ ተቋማዊ ክህደት!
ከላይ የሚታየው ደብዳቤ ዶክተር ሀብታሙ አለሙ ሌሊትና ቀን በቅንነት ሲያገለግለው የነበረው የድል ጮራ ሪፈራል ሆስፒታል ያወጣው የጥሪ ማስታወቂያ ነው። ዶክተሩ በግፍ ታስሮ ፍርድ ቤት እየተመላለሰ መሆኑን፣ ፍትህ ፍለጋ እየናወዘ መሆኑን መላው ህዝብ እያወቀ መሥሪያ ቤቱ አላውቅም ይላል?!😭
መሥሪያ ቤት ለአንድ ሰው ሁለተኛ ቤቱ፣ መከታና ከለላው ነበረ። በሚያጋጥም መከራና ፈተና ሁሉ ቀድሞ ደራሽ፣ ድምፅና ረዳት መሆን ሲገባው፥ ዛሬ እንዳልሰማና እንዳላወቀ ሆኖ እንዲህ ዓይነት የረከሰ ደብዳቤ መጻፍ ፍጹም የህሊና ሞት ነው! ይህንን ግፍ በመፈጸም በጥላቻ የሚረኩ ጥቂት ልባቸው የደነደነ ግለሰቦች ይኖሩ ይሆናል፤ ነገር ግን በመላው ሰራተኛና በጤና ባለሙያው ላይ ታላቅ የደህንነት ስጋትና ጥልቅ ቅሬታ የፈጠረ የክህደት ድርጊት ነው።
የሰው ልጅ ይረሳው ይሆናል፥ ታሪክ ግን ይህንን ግፍ መዝግቦ ለዘላለም ያስቀምጠዋል!!! 💔
#FreeDrHabtamu #JusticeForHabtamu #HumanRightsViolation #ProtectHealthWorkers #Ethiopia #InstitutionalBetrayal