Фотография
click to show
click to show
#JinkaUniversity
በ2018 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የሪሚዲያል ተማሪዎች በሙሉ የማርበርግ ቫይረስ ሙሉ በሙሉ መጥፋቱ በጤና ሚኒስቴር ተረጋግጦ ጥሪ እስከሚደረግላችሁ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁ ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል።
በሌላ መረጃ፤
ከአሪ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች በሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳችሁ የሪሚዲያል ትምህርት ለመከታተል ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ ውጪ በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተመደባችሁ ተማሪዎች ታህሳስ 15 እና 16/2018 ዓ.ም ወደ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ገብታችሁ የ21 ቀናት Quarantine ወስዳችሁ በዩኒቨርሲቲው ነፃ የምግብ እና የመኝታ አገልግሎት እያገኛችሁ በመቆየት ከማርበርግ ቫይረስ ነፃ መሆናችሁ ሲረጋገጥና የምስክር ወረቀት ከተሰጣችሁ በኋላ ወደየተመደባችሁባቸው ዩኒቨርሲቲዎች እንድትገቡ ትምህርት ሚኒስቴር ወስኗል።
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
191 ·