Фотография
click to show
click to show
#ጥቆማ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል የማኅበረሰብ ትምህርት ቤት (AAU-MCS) በማቋቋም በ2019 ዓ.ም ከ1ኛ-7ኛ ክፍል ለማስተማር ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በመሆኑም ልጆቻችሁን በሚከፈተው የማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ማስመዝገብ የምትፈልጉ ወላጆች የሚከተሉትን መረጃዎች ልታውቁ ይገባል፦
የምዝገባ ጊዜ
ከሐምሌ 14-21/2018 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታ
5 ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና ቢዩልት ኢንቫይሮንመንት ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር E04
ትምህርት ቤቱ የሚገኝበት ቦታ፦
5 ኪሎ (በቀድሞው የድኅረ ምረቃ/ፋርማሲ ትምህርት ቤት ግቢ)
የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 1,000 ሲሆን፤ በቀጣይ ወርሃዊ የክፍያ መጠን ይገለጻል ተብሏል።
የሚያስፈልጉ ሰነዶች
● የተመዝጋቢ ልጆች የልደት ካርድ
● ከቀድሞ ትምህርት ቤት ያጠናቀቁበት ሰርተፊኬት
● ሁለት የወላጅ እና አራት የልጅ ፎቶግራፍ
● ወላጆች ህጋዊ አሳዳጊ መሆናቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ
● የክፍያ ደረሰኝ እና የመመዝገቢያ ክላሰር
ትምህርት ቤቱ ቅድሚያ ለዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ልጆች ዕድል የሚሰጥ ቢሆንም፣ ባለው ክፍት ቦታ መሠረት ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ውጭ ላሉ ተማሪዎች በውድድር ተደራሽ የሚሆን መሆኑ ተገልጿል።
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
117 ·