Фотография
click to show
click to show
#EHPLE
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር የሚሰጠውን የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለመውሰድ ከሰኔ 30/2018 ዓ.ም ጀምሮ መረጃችሁን በማስተሳሰር ላይ እንደምትገኙ ይታወቃል፡፡
መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ማስተሳሰር የምትችሉት እስከ አርብ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን ተገንዝባችሁ በ https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (16 Digit FAN) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
🔔 መረጃ የማስተሳሰር ሒደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሒደት ይቀጥላል ተብሏል፡፡
በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን የሚጠበቅባችሁ መሆኑ ተገልጿል።
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
91 ·