Фотография
click to show
click to show
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በመጪው ምርጫ ተሳተፍው ወደትምህርታቸው ይመለሳሉ፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎች በመጪው አገር አቀፍ ምርጫ የሚሳተፉበትን አግባብ በማስመልከት ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስኩላር ልኳል (ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የደብዳቤውን ትክክለኛነት አረጋግጠጧል፡፡)
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሔደው አገር አቀፍ ምርጫ ላይ ተማሪዎች መምረጥ እንዲችሉ፣ የሚሰጠው ትምህርት ከምርጫው በፊት እንዲጠናቀቅና ተማሪዎች ወደ ቤታቸው እንዲሔዱ ታስቦ እንደነበር ሚኒስቴሩ አስታውሷል፡፡
ይሁን እንጂ ይህ አካሔድ በትምህርት አሰጣጥና ጥራት እንዲሁም በተማሪዎች የፈተና ዝግጅትና ስኬታማነት ላይ በሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ምክንያት አስቸጋሪ ሆኖ መገኘቱን ገልጿል፡፡
"ተማሪዎች ሔደው መርጠው ለመመለስ የሚያስፈልጋቸው ቀናት ብቻ ታስቦ እንዲፈቀድላቸውና መርጠው እንደተመለሱ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ" የትምህርት ሚኒስቴር እና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች ከመግባባት ላይ መድረሳቸውን ሰርኩላሩ ጠቁሟል፡፡
በመሆኑም ተማሪዎች በተፈቀደላቸው ቀናት ውስጥ ሔደው መርጠው መመለስ እንዲችሉ ፍቃድ እንዲሰጣቸው ሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱን አሳስቧል፡፡
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
221 ·