Фотография
click to show
click to show
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 ዓ.ም በዘጠኝ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን በኦንላይን መዝግቦ በማወዳደር ለማስተማር ይፈልጋል።
ሚኒስቴሩ ለ2019 የትምህርት ዘመን በ2018 ዓ.ም ትምህርት በጀመረባቸው አምስት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በአራት አዲስ በሚጀምሩ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለማስተማር ይፈልጋል።
በመሆኑም በእነዚህ ዘጠኝ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ተመዝግባችሁ ለመማር የምትፈልጉ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ስለሚኖር ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
የምዝገባ ጊዜው በቀጣይ የሚገለፅ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
156 ·