Фотография
click to show
click to show
#ETA
የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990/2016 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 5 ላይ ብቻ ሀ፣ ለ እና ሐ ተብሎ ተጨምሮ በተዘጋጀው ማሻሻያ ረቂቅ ላይ የትምህርት ማኅበረሰቡ እና ባለድርሻ አካላት እስከ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም ከዚህ በታች በተቀመጡት አማራጮች አስተያየታቸውን እንዲሰጡ ጠይቋል።
https://forms.gle/ndRhodE2yoHSn2P5A ሊንክን በመጫን አስተያየት መስጫውን ማግኘት ትችላላችሁ፤ አስተያየታችሁን ሞልታችሁ ስትጨርሱ (Submit) የሚለውን በመጫን አስተያየታችሁን መላክ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
ማሻሻያ የተደረገበትን ረቂቅ አዋጅ በባለሥልጣኑ ድረ-ገፅ www.neta.gov.et ላይ ማግኘት ይቻላል።
ለሚኖራችሁ ማንኛውም አስተያየት በባለሥልጣኑ ኢ-ሚይል አድራሻ [email protected] ላይ አስተያየታችሁን ሞልታችሁ መላክ ትችላላችሁ ተብሏል።
በአካል ቀርባችሁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን መስጠት ለምትፈልጉ የፊት ለፊት የመወያያ መድረክ በቅርቡ እንደሚያዘጋጅ ባለሥልጣኑ ገልጿል።
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
152 ·