Фотография
click to show
click to show
#ጥቆማ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር ትምህርት ቢሮ ገላን የወንዶች እና እቴጌ መነን የልጃገረዶች መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል በከተማ አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በማወዳደር ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል፡፡
በ2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተምራችሁ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ወደ 7ኛ እና 9ኛ ክፍል የተዘዋወራችሁ ተማሪዎች ለወንድ ተማሪ በገላን የወንዶች መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ለሴት ተማሪዎች በእቴጌ መነን የልጃገረዶች መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በውድድር ለ2019 ዓ.ም ቅበላ ይደረጋል፡፡
ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች በአዳሪ ትምህርት ቤቶቹ ለመግባት መወዳደር የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
(ዝርዝር መስፈርቶችን ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ፡፡)
የምዝገባ ጊዜ
ከሐምሌ 13-17/2018 ዓ.ም
ኦንላይን ይመዝገቡ 👇🏼
● ለገላን ወንዶች አዳሪ መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመልካቾች፦ https://bs.ministry.et
● ለእቴጌ መነን ልጃገረዶች መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመልካቾች፦ https://bs.ministry.et
የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን
● 9ኛ ክፍል ለሚገቡ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም
● 7ኛ ክፍል ለሚገቡ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም
● የፈተና ቦታና ሰዓት በቀጣይ ይገለጻል፡፡
ለበለጠ መረጃ እና
አስተያየት ካለዎት
👇👇👇
[https://t.me/allethioschool]
[https://t.me/allethioschool]
221 ·