ChatCrawlersearch across public Telegram Open the app
E

ETHIO ≈ SCHOOL

2 542 members
28 February 2026
F
Фотография
click to show
#Update የ Speciality ወይም/እና የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ማስተካከያ ቀናት እስከ የካቲት 29/2018 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡ የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ ህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (ERMP) የመግቢያ ፈተና ውጤት መለቀቁ ይታወቃል፡፡ በማስተካከያው ወቅት ተጨማሪ የሬዚደንሲ ( Speciality ) ፕሮግራሞች ያሏቸው ሁለት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል። ➫ የካቲት 12 ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ በ Clinical Radiology (ብዛት 4) ➫ የካቲት 12 ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ በ Otolaryngology-HNS (ENT) (ብዛት 4) ➫ ወሎ ዩኒቨርሲቲ Wollo በ Clinical Radiology (ብዛት 4) ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
635 ·
30 May 2026
Фотография
click to show
#Update የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የጤና ባለሙያዎች ከዛሬ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም ጀምሮ የፈተና ጣቢያ ምርጫ እንድታደርጉ ተብሏል፡፡ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ ወይም በድጋሜ ለመውሰድ ስማችሁን ከፋይዳ ቁጥራችሁ ጋር አስተሳሰራችሁ በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች ከግንቦት 20-26/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የFayda ቁጥራችሁን እና Password በማስገባት የፈተና ጣቢያ እንድትመርጡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡ እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት፣ የፈተና ጣቢያ ምርጫ ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ለብቃት ምዘና ፈተና የመፈተኛ ጣቢያ መምረጥ የምትችሉት ስማችሁን ከፋይዳ ቁጥር ጋር ያያያዛችሁ ተመዛኞች ብቻ እንሆናችሁ ተመላክቷል፡፡ በምዝገባ ወቅት ለሚገጥማችሁ ማንኛውም ችግር በነጻ የስልክ መስመር 952 በመደወል ከዚያም 3 ቁጥርን በመጫን በቀጥታ እገዛ ማግኘት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡ ጤና ሚኒስቴር የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተናን በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም ለመስጠት እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡ ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
235 ·
Фотография
click to show
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018/2019 የመምህራን እና ትምህርት አመራሮች ዝውውር በቀጣይ ቀናት ይፋ እንደሚደረግ አሳውቋል፡፡ የዝውውር ሥራው በጥራት እና ፍትኀዊነትን በጠበቀ መንገድ ሲሰራ መሠራቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
160 ·
Фотография
click to show
#RemedialExamSchedule የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል (አቅም ማሻሻያ) ፕሮግራም ፈተና ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ለአምስት ቀናት እንደሚሰጥ ይታወቃል። በተጠቀሱት ቀናት በሁለት ፈረቃ በጠዋት እና በከሰዓት መርሐግብር የሚሰጠው የሪሚዲያል ፕሮግራም (የተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች) የፈተና መርሐግብር ከላይ ተያይዟል። ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
204 ·
F
Фотография
click to show
Фотография
click to show
የሪሚዲያል ፈተና የመግቢያ ትኬትዎን (Entrance Ticket) እስካሁን አላገኙም?   ተከታዮቹን ቅደም ተከተሎች በመከተል የመግቢያ ትኬትዎን ያውርዱ! ➫ https://verify.ethernet.edu.et ላይ ይግቡ ➫ 'Get your entrance ticket here' የሚለውን ይጫኑ ➫ የመለያ ስምዎን (Username) እና የይለፍ ኮድዎን (Password) ያስገቡ ➫ 'Download Entrance Ticket' የሚለውን ይጫኑ (ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ፡፡)   ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
260 ·
2 June 2026
Фотография
click to show
Фотография
click to show
#AREB   በአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናዎች ከሰኔ 08-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ6ኛ ክፍል ፈተና ➫ ሰኔ 8 እና 09/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ የ8ኛ ክፍል ፈተና ➫ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡   ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
188 ·
F
Фотография
click to show
#MoH ጤና ሚኒስቴር በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ስማችሁን ከፋይዳ ቁጥራችሁ ጋር ያያያዛችሁ ተመዛኞች https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የመፈተኛ ጣቢያ እየመረጣችሁ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ የፈተና ጣቢያ መረጣ እስከ ረዕቡ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ መሆኑን በመረዳት፥ ምርጫችሁን እንድታገባድዱ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። ምዝገባው የማይራዘም መሆኑ ተገልጿል፡፡ ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
192 ·
3 June 2026
Фотография
click to show
#ExitExamSelfVerification የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች በአስቸኳይ የማረጋገጥ ሥራ እንድታደርጉ ተብሏል። የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል ነው። በመሆኑም ለመጀመሪያ ጊዜ የመውጫ ፈተና የምትወስዱ ተፈታኞች የብሔራዊ መታወቂያ FAN ቁጥርዎን በመጠቀምና የግል መረጃ በማማሟላት የራሳችሁን መለያ ማረጋገጫ ማጠናቀቅ ይጠበቅባችኋል። https://verify.ethernet.edu.et/ ከተጫኑ በኋላ Exit Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Continue Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ። የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል። ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
159 ·
Фотография
click to show
#ጥቆማ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ "ሀገር በቀል እውቀት ሥርዓት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማት’’ በተሰኘ የመወያያ ርዕስ የፓናል ውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። መድረኩ በዘርፉ ከፍተኛ ምሁራን አቅራቢነት እና በፕሮፌሰር መንገሻ አድማሱ አወያይነት ይከናወናል። መድረኩ ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 በአዲስ አበባ ቴክኖሎጂና ቢልት ኢንቫይሮመንት ኮሌጅ (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5 ኪሎ ካምፓስ አዳራሽ ይካሔዳል። በአካል መገኘት ለማትችሉ በፖስተሩ ላይ ያለውን QR Code በመጠቀም መከታተል ትችላላችሁ ተብሏል። 🔗 Zoom link: https://us06web.zoom.us/j/88912129718?pwd=dsMHaxcSlsu3cEXXxfnbAT6zWnaIFh.1 👉 Meeting ID: 889 1212 9718 👉 Passcode: 802890 ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
140 ·
Фотография
click to show
Фотография
click to show
👌ብዙ ሰወች የተቀየሩበትን እና እየተቀየሩበት ያሉት Hilton ድርጅትን በመቀላቀል እራስን መለወጥ ይቻላል 👏👏👏👏👏👏👏👏👏 በ አምስት አይነት የገቢ ዓይነቶች ማግኘት ይችላሉ፡- 1. የምርት ገቢ 2. የማሻሻያ ጉርሻ 3. የሪፈራል ጉርሻ 4. የቡድን ኮሚሽን 5. የቪአይፒ ወርሃዊ ደሞዝ እና የነጥብ ሽልማቶች ይህንን ሊንክ  ከተጫኑ በኃላላ https://www.apphlts.com/#/login/469118 https://www.apphlts.com/#/login/469118 1.በመጀመሪያ ስልክ ቁጥር ከ9....... ጀምሮ ማስገባት 2. የማይረሳ የግል passward ማስገባት... ይህን ቁጥር ከ እርስወ ውጭ ማንም ማውቅ የለበትም... ..... ከዛ  #login# የሚለውን መጫን .....ከዚህ በኃላ ሁሉንም ነገር አስረዳ.... በጣም ቀላል እና አዲስ ነው... ፈጥነው ሥራ ይጀምሩ ለበለጠ... ግልፅ ካልሆነለውት...በውስጥ መስመር ያውሩኝ... 👌@yesshsammmits 👌@gashtiman1990
174 ·
F
Фотография
click to show
#RemedialExamProtocols የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ከነገ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት ይሰጣል። የሪሚዲያል ተፈታኞች ሊከተሏቸው የሚገቡ የስነ-ምግባር መመሪያዎች፦ ➫ ተፈታኞች የሞባይል ስልክ፣ ሚሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣ ሳይንቲፊክ ካልኩሌተር፣ የራስ ያልሆነ መታወቂያ እንዲሁም ማንኛውም አይነት የጦር መሳሪያ በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ይዘው መገኘት አይችሉም፡፡ ➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከ3ዐ ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት ክፍል መገኘት አለባቸው፡፡ ➫ ተፈታኝ ተማሪዎች ከተመደቡበት ክፍል ውጪ መፈተን ውጤት ያሰርዛል፡፡ ➫ ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና አስፈጻሚን ትዕዛዝ ማክበር ይጠበቅባቸዋል። ➫ ተፈታኞች የፋይዳ መታወቂያ እንዲሁም ራሳቸውን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ➫ በሌላ ሰው ስም፣ መለያ ቁጥር እና የይለፍ ቃል መፈተን አይቻልም፡፡ ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
160 ·
4 June 2026
Фотография
click to show
#SamaraUniversity   ከሠመራ ዩኒቨርሲቲ ተመርቃችሁ ዋናውን ዲግሪ (Original Degree) ያልወሰዳችሁና እንዲሠራላችሁ የምትፈልጉ የቀድሞ የተቋሙ ምሩቃን፣ ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የመጀመሪያ ዙር ህትመት ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።   በመሆኑም ይህን ሊንክ https://forms.gle/qMwRKY43AQ2RflnX8 በመጠቀም አስፈላጊውን መረጃ እስከ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም በመሙላት እንድትልኩ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።   በወጭ መጋራት የተማራችሁ አመልካቾች ዋናውን ዲግሪያችሁን ለመውሰድ ክፍያ መፈፀማችሁን ወይም በአገልግሎት መወጣታችሁን የሚያረጋግጥ ደብዳቤ እና ደረሰኝ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል ተብሏል፡፡   ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
146 ·
F
Фотография
click to show
Фотография
click to show
Фотография
click to show
#RemedialExam የ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ዛሬ መሠጠት ጀምሯል፡፡ በዛሬው የመጀመሪያ ቀን ፈተና የባዮሎጂ እና ታሪክ ትምህርት አይነት ፈተናዎች በጠዋት እና ከሰዓት ሦስት ፈረቃዎች (2፡00፣ 5፡00 እና 9፡00 ሰዓት) ይሰጣሉ፡፡ ፈተናው ከዛሬ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት ይሰጣል። ምስል፦ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
258 ·
5 June 2026
Фотография
click to show
ለብሔራዊ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ተፈታኞች በሙሉ የተላለፈ መረጃ! እባክዎን ይህንን መረጃ ለሁሉም ተፈታኞች ሼር Share በማድረግ የበኩላችሁን እገዛ አድርጉ። https://gibi-info.yaisoftwares.com?ref=user4312 ከትምህርት ሚኒስቴር ለተላለፈው ይፋዊ ማሳሰቢያ ተጨማሪ ማብራሪያ ይሆን ዘንድ፤ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ራሳቸውን በሚገባ ማዘጋጀት እንዲችሉ የተሠራው የ "Gibi Info" ድረ-ገጽ (Website) ከ100,000 በላይ ጥያቄዎችን የያዘ ነው። መድረኩ ለእያንዳንዱ የትምህርት ክፍል (Department) ከእውነተኛው የኤግዚት ፈተና ጋር የቅርብ ተዛማጅነት ያላቸውን ጥያቄዎች አካቷል። የመመዝገቢያ ሊንክ:- https://gibi-info.yaisoftwares.com?ref=user4312 ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
181 ·
Фотография
click to show
#JimmaUniversity   ጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ ለማክበር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡   ዩኒቨርሲቲው የ75 ዓመታት ጉዞውን በሚዘክረርበት ታሪካዊ ኹነት ላይ የተቋሙ የቀድሞ ተማሪዎች፣ ሠራተኞች እና ወዳጆች እንዲገኙ ጥሪ አድርጓል።   በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የምትገኙ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን እና ወዳጆች፣ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን ኅብረት መስራች አባል እንዲሆኑ ዩኒቨርሲቲው የአለምናይ መመዝገቢያ ድረ ገጽ አዘጋጅቷል።   https://alumni.ju.edu.et/ ላይ በመግባት የአባልነት ቅፁን እንድትሞሉ ተጋብዛችኋል፡፡   ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
156 ·
Фотография
click to show
🔔 የመውጫ ፈተና ተፈታኝ ነዎት? መረጃዎችዎን አረጋግጠዋል? ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ ተማሪዎች በአስቸኳይ መረጃቸውን እንዲያረጋግጡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል ነው። በመሆኑም #ለመጀመሪያ_ጊዜ የመውጫ ፈተና የምትወስዱ ተፈታኞች የFAN ቁጥራችሁን በመጠቀምና የግል መረጃ በማሟላት የራሳችሁን መለያ ማረጋገጫ ማጠናቀቅ ይጠበቅባችኋል። https://verify.ethernet.edu.et/ ላይ ይግቡ፣ Exit Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Continue Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ። ለበለጠ መረጃ እና አስተያየት ካለዎት      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
175 ·
F
Фотография
click to show
Фотография
click to show
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” የተሰኘ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያ አበልፅጎ በሙከራ ደረጃ ሥራ ላይ አውሏል። Agentic AI Teacher Assistant የተባለው መተግበሪያው፣ ሙሉ በሙሉ ያለ ኢንተርኔት የሚሠራ፣ ራሱን ችሎ ውሳኔዎችን ማመንጨት የሚችል እና የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን የሥራ ጫና የሚቀንስ መሆኑ ተገልጿል፡፡ መተግበሪያው በውስጥ አቅም የበለፀገና በአካባቢያዊ ኮምፒውተር (Local Machine) ላይ በቀላሉ ተጭኖ የሚሠራ መሆኑን በሚኒስቴሩ ‎የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ‎ ‎መተግበሪያው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያሉትን መፅሐፍቶች በሙሉ ዳታሴት አድርጎ በመውሰድ፣ መፃሕፍቱን ሙሉ በሙሉ እንዲመረምርና እንዲገነዘብ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል። ‎ ‎መተግበሪያው ምን ምን ይሠራል? ➫ የትምህርት እቅድ (Lesson Plan) ያዘጋጃል፣ ➫ የፈተና ጥያቄዎችና አሳይመንቶችን ያመነጫል፣ ➫ ማስተማሪያ ስልቶችን (Pedagogical Strategies) በራሱ ማቀናጀት ይችላል። መተግበሪያው በማንኛውም ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ ላይ ተጭኖ የሚሠራ ሲሆን፤ ‎በተመረጡ ትምህርት ቤቶች ተሞክሮ አጥጋቢ ውጤት ማስገኘቱ ተመላክቷል፡፡ መተግበሪያውን ለመጠቀም ምንም አይነት ወርሃዊ የኢንተርኔት ካርድ፣ የኔትዎርክ ዝርጋታ ወይም የኤአይ አጠቃቀም ክፍያ እንደማይጠይቅ በሚኒስቴሩ ‎የአይሲቲ አማካሪ ሙሉነህ አጥናፉ (ዶ/ር) አስረድተዋል። ‎ ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ መምህራን እና የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች በመተግበሪያው አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል። ለበለጠ መረጃ      👇👇👇 [https://t.me/allethioschool] [https://t.me/allethioschool]
281 ·
Open in Telegram Feed t.me/s Каталог площадок Искать в ChatCrawler

A snapshot of an open public feed from the search index ChatCrawler — “Google for public Telegram”; refreshed as the venue is crawled. Times are UTC.

Public content only, official Telegram API. About · FAQ · What we do not do · Remove a page · Catalog