#ጥቆማ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሀገር አቀፍ የግእዝ ጉባኤ ከሚያዚያ 15-17/2018 ዓ.ም ያካሒዳል፡፡
ለጉባኤው የሚሆኑ የምርምር ጽሑፎችን ከስር በተገለፁት የምርምር ጭብጦች ዙሪያ እንዲያቀርቡ ተጋብዘዋል፡፡
የምርምር ጭብጦች፦
➫ የጊዜ እሳቤ እና የዘመን መንፈስ በፍልስፍና እና በግእዝ ሥነ ጽሑፍ፣
➫ የዘመን ስሌትና ጥንታዊ የሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚ) ምርምር፣
➫ ሰው መሆን፣ ባህል፣ እምነት እና ጊዜ በግእዝ ሥነ ጽሑፍ፣
➫ የኢትዮጵያ የዘመን ቀመር በግዕዝ ድርሳናት፣
➫ የአቡሻኽር የዘመን አቆጣጠርና የእቆጣጠሩ ብልኃት፣
➫ የዘመን አከፋፈልና የጊዜ እሳቤ በሥነ ተፈጥሮ ጥናት በቅዱስ ያሬድ ሥራዎች፣
➫ የግዕዝ የሒሳብ ስሌት ከዘመናዊ የሒሳብ ስሌት ጋር ሲነፃፀር፣
➫ የግዕዝ ፊደልና ቀመረ ፊደል፣
➫ የገዳማት አስተዋጽኦ በጥንታዊው የዘመን ስሌት፣
➫ የግእዝ ስነ-ጽሁፋዊ ሀብቶች ጥበቃ ከኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር፣
የአኅጽሮተ ጽሑፍ ማስረከቢያ ጊዜ፦
ከታህሳስ 1-20/2018 ዓ.ም
የተመረጡ የምርመር ጽሑፎች ማሳወቂያ ጊዜ፦
ታህሳስ 25/2018 ዓ.ም
ሙሉ ጽሑፍ ለጉባኤው አዘጋጆች የሚላክበት ጊዜ፦
ከመጋቢት 25-30/2018 ዓ.ም
የምርምር ሥራዎች የሚላኩበት አድራሻ፦
➫ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አቶ መኮንን ከፋለ
ስልክ ቁ. 0933225306
ኢሜይል፦
[email protected]
➫ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ የባህል፣ ታሪክ እና ቋንቋ ልማት ማዕከል
ኢሜይል፦
[email protected]
የሚቀርቡ ጥናቶች ከዚህ በፊት ያልቀረቡና ያልታተሙ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ
👇👇👇
[
https://t.me/allethioschool]